4 Click to rate!
based on 23 review(s).
የጥራት አምባሳደር
የጥራት አምባሳደር የጥራት አምባሳደር
Take AddisMap with you - GARMIN Lifetime License The most detailed map of Ethiopia
Target your future customers on AddisMap Lead new customers to you now.
Reserve hotel a hotel room online on AddisMap. Hassle free - online booking in any hotel

ማስታወቂያዎች - Your ad here?

More

የ80 ዓመት ወጣት ቢራ ፋብሪካ

1915 ኮርቶ ዱሮ ሊባል የሚችል ዓመት ነው። የያኔዋ ኢትዮጵያ በንግስተ ነገስታት ዘውዲቱ ምኒሊክ ዘመነ መንግስት ስር ስትሆን አዲስ አበባም ገና አሰርታት ያልደፈነች ወታት ነበረች። ፈረንጆቹ ቱኩል የሚሏቸው የሳር ጎጆ ቤቶቻችን በብዛት የተቸመቸሙባት የያኔዋ አድስ

አበባ ዘመናዊነት፣ የሥልጣኔ ብርሃን፣ አዲስ እድገት፣ ...የሚባሉ ነገሮችን ማስተናገድ መጀመሯ ነው። መንገዶች ተቀይሰዋል፣ መኪኖች ብቅ ብለዋል፣ ዘመናዊ የቤት አሰራሮች ታይተዋል፣ ጋዜጣ መታተም ጀምሯል ተማሪ ቤቶች ተከፍተዋል፣ ባቡርም እየተመመ ነው፣ ወዘተርፈ።

እና፣ እንዲህ መባል በተጀመረበት በዚያን ጊዜ በአዲስ አበባ ከተከናወኑ ዘመናዊ ጉዳዮች አንዱ በመኪና ተጠምቆ በጠርሙስ እየታሸገ የሚሸጥ ጠላ የሚያዘጋጅ ፋብሪካ መቆሙ ነው።"መቼም "አይ ስልጣኔ!" ሳይባልለት አልቀረም። እርግጥ ስለፋብሪካ ነገር፣ በአውሮፓና በአሜሪካ

ስለሚሠሩ ልዩ ልዩ ስራዎች በደንብ የሚያውቁ የሉም ማለት አይደለም። ለብዙዎች ግን በራሳቸው ምድር እንዲህ ዓይነት ተግባር መታየቱ የሚያስደምማቸው ቢሆን አይገርምም። የቅዱስ ጊዮርጊስ ቢራ ፋብሪካ መስራችና ባለቤት ሙሴ ዳዊት ሃል የተባሉ የቤልጂግ ዜጋ መሆናቸውን የፋብሪካው

መረጃዎች ያመለክታሉ። አንዳንድ የፅሁፍ መረጃዎች ደግሞ ባለቤቱ ጀርመናዊ የሆነ ኩባንያ እንደሆነ ይገልፃሉ። ከ43 ዓመታት በፊት በ1952 (እ.ኢት.አ) በታተመው የኢትዮጵያ የንንግድ ጆርናል የሚከተለው ሰፍሮ ይገኛል። ቅዱስ ጊዮርጊስ ቢራ ፋብሪካ በአዲስ አበባ ከተማ፣ ሜክሲኮ አደባባይ፣

20000 ካሬ ሜትር በሆነ ቦታ ላይ ሰፍሮ ይገኛል። ቢራ ፋብሪካው ከ36 ዓመት በፊት በአንድ የጀርመን ኩባንያ የተመሠረተ ሲሆን ከስድስት ዓመታት በፊት ኢትዮጵያዊ የሆነ ኩባንያ ተረክቦታል። Ethiopian Trade Journal, Vol.1, No.1, August 1960:21

እርግጥ ፋብሪካው የተመሰረተው በሙሴ ዳዊት ሃል ሲሆን እኚህ ሰው ወደ በኋላ ለአንድ የጀርመን ኩባንያ ሸጠውታል። ፋብሪካው የተቆረቆረው በዚያው ዛሬ በቆመበት ስፍራ ነው። በንጉሰ ነገስቱ ማርሻል ሽሙት ጎዳና ተብሎ ነበር የሚታወቀው። ጎላ ጎላ ያለና ለዓይን የሚሞላ ህንፃ አዘጋጅቶ ስራውን

ሲጀምር በኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ልማት የመጀመሪያ ምዕራፍ ከፋች ከሆኑት ጥቂት ኢንዱስትሪዎች አንዱ ለመሆን በቅቷል። ፋብሪካው ስራ ሲጀምር አብዛኛው የስራ ሂደት የሚከናወነው በሰው ቀጥተኛ ጉልበት በእጅና በእግር በሚዘወሩ መሳሪያዎች ነበር። ጥሬ ዕቃዎችን ከማጓጓዝና ወደ ቋት

ከማስገባት ጅምሮ ድፍድፉን የማብላላቱ፣ የቢራ ገብሱን የመቀቀሉ፣ ቢራውን የማጣራቱና የማጥለሉ፣ የተጣራውን ቢራ በጠርሙስ እየሞሉ የማሸጉ፣ ወዘተርፈ ተግባራት ሁሉ የሰራተኞችን ቀጥተኛ ጉልበት የሚፈልጉ ነበሩ። የቢራ መሰረታዊ ግብዓቶች የሆኑት ቢራ፣ ገብስና የቢራ ጌሾ ከውጭ

አገሮች ነበር የሚቀርቡት የፋብሪካውን የበላይ ማኔጅመንትና የጠመቃውን ሂደት የሚቆጣጠሩ የቴክኒክ ባለሙያዎችም እንኳን ባእዳን ዜጎች ነበሩ። በመጀመሪያዎቹ የምርት ዓመታትም በቀን ይመረት የነበረው 200 ያህል ጠርሙስ ቢራ እንደሆነ ይነገራል። በዚያን ዘመን በአዲስ አበባ የመጠጥ ቤቶች

አልተስፋፉም፣ ኅብረተሰቡ በየቤቱ የሚጠመቅ ጠላና ጠጅ ይጠጣ እንደሁ እንጂ እንደዚህ እንዳሁኑ ዘመን መጠጥ ለመጠጣት ተብሎ የሚኬድባቸው ቦታዎች አልነበረም። የቀድሞውን ሁኔታ ሰምተናል የሚሉ አንጋፋ ሰራተኞች እንደሚጠቁሙት በመጀመሪያዎቹ ዓመታት የቢራ ምርቱ ይቀርብ የነበረው

ለቤተመንግስቱ መኳንንት ነበር። ፋብሪካው በዚህ ሁኔታ ስራውን ቀጥሎ ሳለ ኢጣሊያ ኢትዮጵያን ወረረች፡፡ አንዳንድ እርግጠኛ ያልሆኑ መረጃዎች በዚህ ወቅት ፋብሪካው ተዘግቶ እንደነበር ይገልፃሉ።


የኢትዮጵያ ነፃነት ከተመለሰ በኋላ በነበሩት ዓመታት ፋብሪካው የማምረት ሥራውን የቀጠለ ሲሆን የባለንብረትነት መብትን የተመለከቱ ውዝግቦች ተነስተውበት ነበር። የውዝግቡ ትክክለኛ ይዞታ የሚታወቅ ባይሆንም በ1945/6 ፋብሪካው ወደ ኢትዮጵያዊ ኩባንያ መዛወሩን የሚገልፁ የፅሁፍ

መረጃዎች አሉ። ይህ ኢትዮጵያዊ ኩባንያ በአክስዮን የተደራጀ ሆኖ ከፍተኛው ድርሻ የቀዳማዊ ኃ/ሥላሴ ነበር። የቅዱስ ጊዮርጊስ ቢራ ፋብሪካ ከነፃነት መመለስ በሁዋላ ባሉት መልካም እድገት ሲያሳይ ቆይቷልማለት ይቻላል። በ1950ዎቹ መጀመሪያ የነበረው ዓመታዊ የምርት መጠን በዓመት

50000 ሄክቶ ሊትር ያህል ነበር። በፋብሪካው እያንዳንዳቸው 100 ሄክቶ ሊትር ያህል ሊይዙ የሚችሉ 53 ጋኖች እንደሚገኙ፣ በፈረቃ 24 ሰዓታት የሚሰሩ 300 ያህል ሰራተኞች እንደነበሩና የቢራ ምርቱ በፋብሪካው የማጓጓዣ መኪናዎች በመላው አገሪቱ በመሰራጨት ላይ እንደነበር ኢትዮጵያዊ

የጠመቃ ስራ ማስተር (ብሩው ማስተር) ሥራው እንደሚመራ፣ ወዘተርፈ ከፍ ሲል የተጠቀሰው ምንጭ ያቀረበቅ ዘገባ ያስረዳል። በዚህ ወቅትም የቀድሞ የማምረቻ መሳሪያዎቹ ቀስ በቀስ ወደ ገሚስ አውቶማቲክነት ተቀይረው በወቅቱ ፋብሪካው ዘመናዊ ከሚባል ደረጃ ቢደርስም ብዙ ስራዎች

የሚከናወኑት በሰው ጉልበት ነበር። ትውስታቸውን ካካፈሉን ነባር ሰራተኞች መካከል በ1953 የተቀተሩት አቶ ሐዲስ ነጋሽ ጣሰው በዚያን ዘመን ስለነበረው የፈብሪካው ገፅታ ሲገልፁ ያነሱዋቸው ጉዳዮች ሁኔታውን ይበልጥ ያስረዳሉ። ... በዚያን ጊዜ እንዳሁኑ በኤሌክትሪክ ኃይልና በነዳጅ

የሚንቀሳቀሱ ቦይለሮች አልነበሩም። ለሙቀት ክፍሉ የእሳት ማንደጃ የሚማገደው ግንዲላ በጥም ከባድ ሲሆን፣ በተለይ በሚማገድበት ጊዜ የእሳቱ ወላፈን እጅግ ኃይለኛ በመሆኑ እስከ ሶስት ሜትር ድረስ ቃጠሎው ይሰማን ነበር። በዚያን ጊዜ አጠቃላይ የፋብሪካው ሥራ ሙሉ በሙሉ በሰው ጉልበት

ስለሚከናወን ስራው እጅግ አድካሚና አስቸጋሪ ነበር። ለጠመቃ የሚውል ኩንታል ገብስ ተሸክሞ ፎቅ መውጣት፣ ለመቅጃ ክፍል የሚቀርበውን ባዶ ጠርሙስ ከማጠብ ጀምሮ ታሽጎ እስኪወጣ ድረስ ከቦታ ቦታ የማጓጓዝና ሌሎችም የምርት ተግባሮች ሁሉ የሚከወኑት በሰው ኃይል በሸክም ብቻ ነበር።

ሰራተኞች ወደመደበኛ ስራቸው ሳይሰማሩ በፊት በነፍስ ወከፍ አስራ አምስት ኩንታል ገብስ እየተሸከሙ ፎቅ በመውጣት ለወፍጮ በየቀኑ ማቅረብ የዕለት ግዳጃቸው ነበር። በዚያን ጊዜ ቢራው ወደ እያንዳንዱ ጠርሙስ የሚሞላው በሰው ኃይል በሚሽከረከር ባለአምስት ጡት መቅጃ ነበር። ቆርኪም

በሰው እጅ በሚንቀሳቀስ መሳሪያ ይከደናል። ጠርሙስ የሚታጠበው በገንዳ ተዘፍዝፎ አድሮ በብሩሽ እየተፈገፈገ ነበር። ..." በዚህ ሁኔታ ምርቱን የቀጠለው ቅዱስ ጊዮርጊስ ቢራ ፋብሪካ በ1966ቱ አብዮት መዳረሻ በመሳሪያዎቹ ደረጃ፣ በተሽከርካሪዎች አገልግሎት፣ በህንፃዎች፣ እንዲሁም በሽያጭ

አውታሮች ስፋት መልካም አቋም ነበረው። ፋብሪካውን ለማስፋፋትና ተጓዳኝ የለስላሳ መጠጥ ምርት ለመጀመርም አቅዶ ነበር። ፋብሪካው በ1966 ወደመንግስት ይዞታነት እንዲዛወር ተደረገ። ይህ በፋብሪካው አሰራር ላይ አንዳንድ ችግሮችን ቢፈጥርም አንዳንድ መልካም እርምጃዎችን እና መሻሻሎችን

አሳይቷል። በተለይ በሰው ኃይል አቅሙና አስተዳደር ረገድ ዓይነተኛ እድገት አስመዝግቧል። በምርት አቅጣጫም በ1969 በአገሪቱ ተወዳጅ የሆነውንና ሰፊ ገበያ ያለውን የድራፍት ቢራ አገልግሎት ለመጀመር ችሏል። ፋብሪካው በመንግስት ይዞታ ስር በነበረ ጊዜ የፋይናንስና አስተዳደራዊ ችግሮች ስለነበሩበት

በዓለም ደረጃ ከ1970ዎቹ ወዲህ በቢራ ተመቃ ቴክኖሎጂ በኩል የተገኙ ፈጥን ርምጃዎችን ተከትሎ ለመጓዝ አዳግቶት ቆይቷል። የፋብሪካው ስያሜም ተቀይሮ ነበር። በ1970ዎቹ ዓመታት አንድ ጊዜ ፒልስነር ቢራ ፋብሪካ ተብሎ ነበር። ፋብሪካው እነዚህን የመሰሉ ችግሮች ቢያጋጥሙትም፣ በሌላ

በኩል ደግሞ የፋብሪካው ስምና ምርት ተወዳጅ ሆኖ እንዲቀጥል ለማደረግ ችለዋል። የቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ክለብን ጨምሮ ሌሎች ማህበራዊ እንቅስቃሴዎችን በመደገፍ፣ በማበረታታትና በማጎልበት ፋብሪካው የተጫወተው ሚናም ከፍተኛ ነው።


በአሁኑ ወቅት ኢትዮጵያ በምትከተለው አዲስ የነፃ ገበያ ኢኮኖሚ ሥርዓት መሰረት ፋብሪካው እንደቀድሞው ወደግል ይዞታ እንዲዛወር ተደርጓል። አሁን የቅዱስ ጊዮርጊስ ቢራ ፋብሪካ ባለንብረት ቢ.ጂ.አይ. የተባለ ዓለም ዓቀፍ የቢራ ጠማቂ ኩባንያ ነው። ቢ.ጂ.አይ. በዓለማቀፍ ደረጃ ታዋቂ

የሆነ፣ በልዩ ልዩ አገሮች የቢራ ፋብሪካዎችን ከፍቶ የሚያመርት ፣ ዘመናዊ የሆነና የላቀ የጥራት ደረጃ ያለውን ቢራ በማምረት በዓለም የቢራ ገበያ ከፍተኛ ስም ያተረፈ ኩባንያ ነው። የቅዱስ ጊዮርጊስ ቢራንም ወደዚሁ የላቀ የጥራት ደረጃ አሸጋግሯል። ዛሬ የቅዱስ ጊዮርጊስ ቢራ በኢትዮጵያ

ነባር ቢሆንም ፍፁም ዘመናዊና ወጣት ነው።


አንዳንድ መረጃዎች ስለ ቢ.ጂ.አይ ኢትዮጵያ

ቢ.ጂ.አይ ኢትዮጵያ 3 /ሶስት/ የቢራ ፋብሪካዎች/ አዲስ አበባ፣ ኮምቦልቻ፣ ሐዋሳ ሲኖሩት አንድ የወይን ጠጅ ፋብሪካ በዝዋይ በመስራት ላይ ይገኛል።

የሰራተኛ ብዛት:-

ቅዱስ ጊዮርጊስ ቢራኮምቦልቻካስቴል ዋይነሪሀዋሳ ቢራድምር
ቋሚ523367992431232
ጊዜያዊ2282337742501485
ድምር7516008734932,717







የተከፈለ ታክስ (በሚልዮን ብር)

የታክስ ዓመት20092010
ኤክሳይዝ ታክስ254367
ተጨማሪ እሴት ታክስ232233
የትርፍ ታክስ138600
ከስተምስ /Customs Duty/36600
ሱር ታክስ32600
ድምር692600











የሽያጭ መጠን፦ በብር ተጨማሪ እሴት ታክስን ሳይጨምር

20091,548,000,000
20101,676,000,000

አድራሻችን

ቢ.ጂ.አይ ኢትዮጵያ ኃላ.የተ.የግ.ማህ (ኢንዱስትሪ)


Addis Ababa, Ethiopia

GPS: Lat 9.011666 / Lon 38.742482

Around here:

አቅጣጫዎች

Map: How to find us.
Embed this map in your page

Copy this HTML code to your page:

Reviews

  • ቢ.ጂ.አይ ኢትዮጵያ ኃላ.የተ.የግ.ማህ (ኢንዱስትሪ) 5
    by
    Hello, my name is Tolessa i am very interested in BGI plc industry. Now I am undergradute student, i am very interested to do my internship with this industry.The St. George Brewery is some what known relative to other bevarege, so its best to make this brewery most popular in this country. Do the best.
  • ቢ.ጂ.አይ ኢትዮጵያ ኃላ.የተ.የግ.ማህ (ኢንዱስትሪ) 4
    by
    currently, I am living in Jimma town, yet I am from Addis. for the last 12 years in Jimma, I did not use/drink any other beers. now st George is being ignored by many in Jimma and the other local beer, Bedale, is more preferable almost by all users. I think st George misses promotion strategy and quality?
  • ቢ.ጂ.አይ ኢትዮጵያ ኃላ.የተ.የግ.ማህ (ኢንዱስትሪ) 5
    by
    Hi I ask to import your beer St set gorge to iIsrael Please get contact with me
  • ቢ.ጂ.አይ ኢትዮጵያ ኃላ.የተ.የግ.ማህ (ኢንዱስትሪ) 1
    by
    I think BGI Ethiopia aim is to grow with Ethiopia, empowering its employees to be the best at what they do – every day! they will continue to excite their consumers and grow their brands to make them the most preferred in the country. you love developing the people because you get energy from it selves. you are role models in terms of your behaviors. BGI is the beast company since established. I am a microbiologist I want to Join our company. and BGI ethiopia i just want to give you a comment on your company. as we all know you are the leading brewer in the country:but,you still don't have non alcoholic beverage. why not? And next, i want to ask if you have position for fresh graduates of applied microbiologist,
  • ቢ.ጂ.አይ ኢትዮጵያ ኃላ.የተ.የግ.ማህ (ኢንዱስትሪ) 5
    by
    BGI is an icon for Knowers' and users' of Ethiopian Beer. you are the leading brewer in the country
  • ቢ.ጂ.አይ ኢትዮጵያ ኃላ.የተ.የግ.ማህ (ኢንዱስትሪ) 4
    by
    Dear BGI brewers i am a chemical engineering student in debreberhan university and had been accepted to shandong university in china but i can't afford the fee and i am hoping BGI to sponsor my scholarship. and i i will be paying back by working for your company
  • ቢ.ጂ.አይ ኢትዮጵያ ኃላ.የተ.የግ.ማህ (ኢንዱስትሪ) 5
    by
    Truly Ambassador of quality. I love St George beer.
  • ቢ.ጂ.አይ ኢትዮጵያ ኃላ.የተ.የግ.ማህ (ኢንዱስትሪ) 4
    by
    You guys are doing great, you just need a new innovative methods to interact with people on a daily basis. Other than that I love St.George beer.
  • ቢ.ጂ.አይ ኢትዮጵያ ኃላ.የተ.የግ.ማህ (ኢንዱስትሪ) 5
    by
  • ቢ.ጂ.አይ ኢትዮጵያ ኃላ.የተ.የግ.ማህ (ኢንዱስትሪ) 5
    by
    I think BGI Ethiopia aim is to grow with Ethiopia, empowering its employees to be the best at what they do – every day! they will continue to excite their consumers and grow their brands to make them the most preferred in the country. you love developing the people because you get energy from it selves. you are role models in terms of your behaviors. BGI is the beast company since established. I am a mechanical engineer I want to Join our company.
  • ቢ.ጂ.አይ ኢትዮጵያ ኃላ.የተ.የግ.ማህ (ኢንዱስትሪ) 1
    by
    I'm a student of university in Addis Ababa. I like BGI. It used to be my dream to work there until i did my research paper for my BA degree. They wouldn't cooperate with me to distribute my questionnaire. Now my graduation got postponed to the next year because of the secretary. I would be glad if the manager takes a good look at the employees not only because of my questionnaire, but also for other students, inverster etc. I'm extremely disappointed at BGI.
  • ቢ.ጂ.አይ ኢትዮጵያ ኃላ.የተ.የግ.ማህ (ኢንዱስትሪ) 5
    by
    Dear BGI, I come up with the idea of cost reduction in which it's very essential for every business. what I mean is why don't you cut down your travel cost by signed a corporate agreement contract with Kenya airways. we have so amazing upfront & Back end discounts which you should to look at it and may consider. Let's talk about it , give me the chance to explain how my product will solve your travel problems. I look forward to hear from you soon, Kindest regards, Tewodros
  • ቢ.ጂ.አይ ኢትዮጵያ ኃላ.የተ.የግ.ማህ (ኢንዱስትሪ) 1
    by
    I live Washington DC and I know many most restaurants who are having a trouble experience with distributor who has horrible attitude. It's sad to Know BGI only had ONE person distribute beer in United State.
  • ቢ.ጂ.አይ ኢትዮጵያ ኃላ.የተ.የግ.ማህ (ኢንዱስትሪ) 5
    by
    Foreign investment in Ethiopia's beer industry is showing a huge increase as global groups are increasingly attracted to the industry and multinational beer companies are continuing to increase their presence in rapidly growing economy. BGI, Dashen, Heineken, Meta, Raya, Habesha and Zebidar are the seven beer companies operating in Ethiopia which collectively run 11 factories. Four giant liquor and two wineries also make part of Ethiopia's growing beverage industry. Since the industry is extremely competitive pursuing Effective supply chain management is the best methodology to reduce costs, increase customer satisfaction, better utilize assets, and build new revenues To remain competitive and to sustain growth, brewery companies would need to watch out for the trends that will shape the industry over the next few years and understand the challenges so that they may be able to potentially turn them into opportunities.
  • ቢ.ጂ.አይ ኢትዮጵያ ኃላ.የተ.የግ.ማህ (ኢንዱስትሪ) 5
    by
    Dear BGI brewers; I am recently joined MSc Program in Industrial Engineering and Logistics Management; and well i am interested in supply chain management and operations research emerging principles which is widely applicable in recent day brewing ventures. I hope you are thinking of it since BGI is big and needs to be big. Thanks
  • ቢ.ጂ.አይ ኢትዮጵያ ኃላ.የተ.የግ.ማህ (ኢንዱስትሪ) 4
    by
    With your innovations, we accept enjoyment to our life in many new ways.you will keep enthusing and surprising your consumers, we are continuously looking for your innovation
  • ቢ.ጂ.አይ ኢትዮጵያ ኃላ.የተ.የግ.ማህ (ኢንዱስትሪ) 5
    by
    dear sirs, i would like to import your beer to Lebanon and i need an email so i can send you my inquiry in order to get a quotation kindly advice.
  • ቢ.ጂ.አይ ኢትዮጵያ ኃላ.የተ.የግ.ማህ (ኢንዱስትሪ) 4
    by
    your is one of the best beer in ethiopia and but u need to advetise it more because it might be lost in comptition with other beers
  • ቢ.ጂ.አይ ኢትዮጵያ ኃላ.የተ.የግ.ማህ (ኢንዱስትሪ) 4
    by
    Hi BGI ethiopia i just want to give you a comment on your company. as we all know you are the leading brewer in the country:but,you still don't have non alcoholic beverage. why not? And next, i want to ask if you have a junior training packages for fresh graduates of chemical engineering, and your university-industry link. see you
  • ቢ.ጂ.አይ ኢትዮጵያ ኃላ.የተ.የግ.ማህ (ኢንዱስትሪ) 3
    by
  • ቢ.ጂ.አይ ኢትዮጵያ ኃላ.የተ.የግ.ማህ (ኢንዱስትሪ) 3
    by
    Hello BGI company employee and employers I am just giving the feedback for your organization. the organization have a lot of basic and fundamental issue that a thought last year 1. It encourage the people that might forgotten by the rest of the people. 2. It support the Ethiopian people those could not help them selfs BUT I didn't see if it can support scholarship
  • ቢ.ጂ.አይ ኢትዮጵያ ኃላ.የተ.የግ.ማህ (ኢንዱስትሪ) 5
    by
    I am just considering myself not as beneficiary of the product rather thinking as Agent the product. I do have close contact with Western Cluster Promoters, Sales and technicians. But we also talking each other on issue sponsoring in Millions & Billions for the Ethiopian Signers. BGI is an icon for Knowers' and users' of Ethiopian Beer. Why not deserve for public utilities in line with Community and government demands instead of....? I will say keep it up the remaining all marketing activities. best
  • ቢ.ጂ.አይ ኢትዮጵያ ኃላ.የተ.የግ.ማህ (ኢንዱስትሪ) 4
    by
    I am just considering myself not as beneficiary of the product rather thinking as Agent the product. I do have close contact with Western Cluster Promoters, Sales and technicians. But we also talking each other on issue sponsoring in Millions & Billions for the Ethiopian Signers. BGI is an icon for Knowers' and users' of Ethiopian Beer. Why not deserve for public utilities in line with Community and government demands instead of....? I will say keep it up the remaining all marketing activities. best

Your Feedback

Tell us about your experience at this place.
For example your first name - this is how the review will be published.
Will not be published.
Will not be published. Required to send your gift.